Tuesday, 29 December 2015

እኛና ታላቁ የህዳሴ ግድብ

ታረቀኝ ዘነበ  
 
    
       
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የግንባታ ሥራን ለማስቆም በግብጽ መንግስት ፖለቲከኞች፣ ምሁራንና መገናኛ ብዙሃን መሣሪያነት የዋሉት በርካቶች ቢሆኑም፤ “ድሆች ናቸው” ከሚለው እስከ ማስፈራሪያ ዛቻዎች ድረስ ጥቅም ላይ እንዲውሉ ማድረጋቸው የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፡፡ 
በግብፅ በተከሰተው ፖለቲካዊ ቀውስ ሳቢያ ከሙባረክ እስከ ሙርሲ ብሎም እስከ አሁኑ በፊልድ ማርሻል አል-ሲሲ የሚዘወረው ጊዜያዊ መንግስት ድረስ በርካታ ገዥዎች በትረ ስልጣኑን ቢቆናጠጡም፤ በዓባይ ውኃ ላይ የሚያራምዱት አስተሳሰብ ግን ልዩነት የተስተዋለበት አይመስለኝም፡፡ 

ይልቁንም የፖለቲካ አስተሳሰባቸውን ወደ ጎን በማድረግ የዓባይ ጉዳይ የህዝባቸው የመኖርና ያለመኖር ጉዳይ እንደሆነ ያለ ልዩነት ሲናገሩ እየተደመጡ ዛሬ ላይ መድረሳቸውን አስረጅ የሚያስፈልገው አይመስለኝም—ሲከውኑት የነበሩት ተግባሮቻቸው አፍ አውጥተው ይናገራሉና። ለህዝባቸው ጥቅም መረጋገጥም ሽንጣቸውን ገትረው መከራከሩን ብሔራዊ አጀንዳቸው አድርገው መቀጠላቸውም እንዲሁ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የሀገራችንን የህዳሴ ጉዞ የማሳካት፣ ሀገራዊውን የፀረ - ድህነት ትግል ከዳር የማድረስ ከፍተኛ ድርሻ ያለውና ከድህነት መውጫ መሰላል የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለመላው ኢትዮጵያዊ የህይወት ጉዳይ መሆኑ ለድርድር የማይቀርብ ቢሆንም፤ በሀገራችን ፖለቲከኞች፣ ምሁራንና መገናኛ ብዙሃን በኩል ብሔራዊ አጀንዳ አድርጎ ከመንቀሳቀስ አኳያ ግን ውጤታማ መሆኑን ለመናገር የሚያስደፍር አይመስለኝም፡፡ 

Sunday, 27 December 2015

ከሁከቱ ምን አተረፍን ?




ዮናስ
መነሻውን የአዲስ አበባባና በዙሪያዋ የሚገኙ ከተሞችን የተቀናጀ ፕላን በማድረግ በአንዳንድ የኦሮሚያ ከተሞች በተማሪዎች የተጀመረው ተቃውሞ በተወሰኑ አካባቢዎች መልኩን እየቀየረ ወደ ሁከት በመምራቱ መንግስት አስፈላጊውን እርምጃ እየወሰደ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህንኑ ተከትሎ ታዲያ ስለሃገራችን ጸጥታ ደንታ የሌላቸውና ይልቁንም አበረታች እንደሆኑ የሚታወቁቱ ሁሉ የመግለጫ ጋጋታውን ተያይዘውታል፡፡


መንግሥት በኦሮሚያ የተነሳውን መጠነ ሰፊ ተቃውሞ ለማርገብ ያልተመጣጠነ ኃይል ከመጠቀም እንዲቆጠብ በማለት ያሳሰበውና የለመድነው ደግሞ አምነስቲ የተሰኘው ነው፡፡
አምነስቲ ኢንተርናሽናልና ሂውማን ራይትስ ዎች ሰሞኑን በጉዳዩ ላይ ባወጡት መግለጫ፤ መንግስት ተቃውሞ በሚያሰሙ አካላት ላይ ያልተመጣጠነ ኃይል ከመጠቀም እንዲቆጠብ ጠይቀዋል፡፡ መንግሥት የዜጎችን ሃሳብን በነፃነት የመግለፅና ሰላማዊ ተቃውሞ የማድረግ መብት ከማክበር ይልቅ ጉዳዩን ከሽብርተኝነት ጋር ማያያዙ አግባብ አይደለም ብሏል አምነስቲ፡፡ የነዚሁ ድርጅቶች አጃቢ እና አራጋቢው መድረክ ደግሞ እንዲህ አለ፡፡
ተቃውሞውን ተከትሎ በተፈጠረው ግጭት 32 ሰዎች በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች መገደላቸውን ያስታወቀ ሲሆን አምነስቲ ኢንተርናሽናል የሟቾች ቁጥር ወደ 40 እንደሚጠጋ ገልጿል። የሙሾው ተቀባይ ደግሞመንግሥት ተቃውሞ ያሰሙትን ሁሉ በሽብርተኝነት ፈርጇል ከህግ አግባብ ውጪ በፀጥታ ኃይሎች የሚፈፀምን ግድያ ከማውገዝ ይልቅ ተቃዋሚዎቹን ሽብርተኛና ሀገር ሊበጠብጡ የተነሱ ናቸው ማለቱ አግባብ አይደለም ሲል ተቃውሟል። የውዝግቡ መነሻ ከሆነው ማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ 2006 . ተመሳሳይ ግጭት ተፈጥሮ የበርካቶች ህይወት ጠፍቶ እንደነበር ያስታወሰው ሂውማን ራይትስ ዎች በበኩሉ፤ ያኔም ሆነ አሁን በተነሳው ተቃውሞ በርካቶች መገደላቸውን፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ መታሰራቸውን አስታውቋል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት በተነሳው ተቃውሞ አብዛኞቹ የተቃውሞው ተሳታፊዎች ተቃውሞ ስላቀረቡ ብቻ ጉዳዩ ከሽብር ተቆጥሮ በሽብር እንደተፈረደባቸው የጠቀሰው ሂውማን ራይትስ ዎች፤ በወቅቱ ታስረው የነበሩ ተማሪዎች በእስር ቤት ውስጥ ግርፋትና ስቃይ ደርሶባቸዋል ብሏል፡፡ ከሦስት ሳምንታት በላይ ለዘለቀው ተቃውሞ መንግሥት የፀጥታ ኃይሎቹ ከመጠን በላይ ኃይል እንዳይጠቀሙ ሊከላከል ይገባ ነበር ያለው "የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ" ህግ የጣሱ አካላት በገለልተኛ ወገን ተጣርቶ ተገቢውን ቅጣት ማግኘት አለባቸው ብሏል፡፡

Monday, 30 March 2015

ስኬታማው የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲና ስትራቴጂ







 ኢህአዴግ የተከተለው ትክክለኛ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲና ስትራቴጂ በግብርናና ገጠር ልማት አንጸባራቂ ስኬቶች እንዲመዘገቡ አስችሏል!!

የተከበራችሁ የአገራችን ህዝቦች!
ባለፉት 23 አመታት በኢህአዴግ ትክክለኛ ፖሊሲና ቁርጠኛ አመራር እመርታዊ ስኬቶችና ለውጦች ከተመዘገገበባቸው መስኮች ውስጥ የግብርናና የገጠር ልማት አንዱ ነው፡፡ ያለፉት ስርአቶች በተከተሉት ጸረ ዴሞክራሲያዊ አገዛዝና የተሳሳተ ፖሊሲ ለአራችን እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሊያበረክት ይችል የነበረውን የግብርና ዘርፍ አምክነውታል፣ የአገራችን ህዝቦችንም ለስቃይና ለሰቆቃ ኑሮ ዳርገዋቸው ነበር፡፡ እንደሚታወቀው የፊውዳል ስርዓት ማቆጥቆጥን ተከትሎ መሬት በአገራችን ቁልፍ የኢኮኖሚ የፖለቲካ ጥያቄ ሆኖ ቆይቷል። በፊውዳሉ ስርዓት የገዢ መደቦች የፖለቲካ ስልጣናቸውን ተጠቅመው የአርሶ አደሩን መብት ረግጠው ጉልበቱንና ምርቱን በመመዝበር የመከራ ህይወትን ሲገፋ ኖሯል። አርሶ አደሮች ላባቸውን አንጠፍጥፈው ያመረቱትን ምርት በፊውዳሎች እየተቀሙ የበይ ተመልካች ሆነው ለረጅም ዘመናት ኖረዋል፡፡ የንጉሱ ስርአት እንዲወገድ ካደረጉት የህዝቦች መሰረታዊ ጥያቄዎች ውስጥ የመሬት ላራሹ ጥያቄ አንዱ ነበር፡፡ 
የአገራችንን ህዝቦች የትግል ውጤት በሃይል ቀምቶ በፊውዳሉ ስርዓት እግር የተተካው የደርግ አገዛዝ የመሬት ጉዳይ የኢትዮጵያ ህዝብ ዋነኛ ጥያቄ መሆኑን ስለተረዳ ለይስሙላ “መሬት ላራሹ” ብሎ ቢያውጅም በተጨባጭ የፈፀመው የዚህን ተቃራኒ ነበር። ደርግ የወሰደው ጥገናዊ ለውጥ የህዝቦችን የመብት ጥያቄዎች ሳይመልስ የተካሄደ በመሆኑ ቅርጹንና መልኩን ቀይሮ ጭቆናውን ያስቀጠለ ነበር፡፡ ደርግ የአርሶ አደሩ ጉልበትና ምርት በመበዝበዝ በአንድ በኩል የአርሶ አደሩ አቅም እንዲዳከም በሌላ በኩል የራሱን ወታደራዊ አቅም እንዲጎለብት አቅዶ ሰርቷል። በየአካባቢው የእርሻ ሰብል ግብይት ድርጅቶችን በማቋቋም አርሶ አደሩን ያመረተውን ምርት ኮታና የዋጋ ተመን በማውጣት በርካሽ ዋጋ ለመንግስት እንዲሸጥ፣ ኋላም የራሱን ምርት መልሶ ከመንግስት በውድ ዋጋ እንዲገዛ ግዳጅ ጥሎበት ነበር። በወቅቱ መንግስት ባወጣው የዋጋ ተመንና ኮታ መሰረት ከአርሶ አደሩ የገዛውን ምርት በእጥፍ እያተረፈ ሲሸጠው የነበረ ሲሆን ይህም ስርአቱ ምን ያህል በዝባዥ እንደነበረ ያሳያል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ህዝቡ በማያምንባቸው ለጦርነት የሚውል ገንዘብ እንዲያዋጣ ይገደድ ነበር፡፡ በተጨማሪም የፊውዳሉም ሆነ የደርግ ስርዓት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአገራችንን አርሶ አደሮች ህይወት ሊቀይሩ የሚችል ትክክለኛ ፖሊሲና የአመራር ድጋፍ መስጠት የሚችሉም የሚፈልጉም አልነበሩም።

የእነዚህ ችግሮች ድምር ውጤት አርሶ አደሩ ለበርካታ ዓመታት በአስከፊ ችግር ውስጥ እንዲቆይ፣ የግብርናው ዘርፍም ከእጅ ወደ አፍ የሆነ የአመራረት ዘይቤ እንዳይላቀቅ አድርጎታል፡፡  ይህ ያለፉት መንግሥታት የተሳሳተ አቅጣጫ አርሶ አደሩን ብቻ ሳይሆን መላ የአገራችንን ህዝቦች ወደ አዘቅት የከተተ በመሆኑ የረጅም ጊዜ ስልጣኔ ታሪክ ባለቤት የነበረችው ሀገራችን በአስከፊ ድህነት፣ ኋላቀርነትና ድንቁርና ልትማቅቅ ግድ ሆኖባታል። ለዚህም ነው ይህን አስከፊ አገራዊ ገጽታና በህዝቦች ላይ የደረሰ ዘግናኝ በደል ለመቀየር የአገራችን ህዝቦች የትውልዶችን ቅብበሎሽ በጠየቀና ከፍተኛ መስዋዕትነት በተከፈለበት ትግል ስርቶቹን ያስወገዷቸው።
የተከበራችሁ የአገራችን ህዝቦች!
ከአገራችን ነባራዊ ሁኔታ አኳያ ለረጅም ዘመናት ከኖርንበት ድህነት ለመውጣት ከህዝብ ጉልበትና ከመሬት የተሻለ የልማት ግብዓት ሊኖር እንደማይችል ኢህአዴግ በጥብቅ ያምናል። ኢህአዴግ ይህን ነባራዊ ሀቅ በሚገባ በማጤን በፕሮግራሙ ሰፊውን የአገራችንን አርሶ አደርና አርብቶ አደር ለሚያሳትፈው የግብርናና ገጠር ልማት ዘርፍ አመቺ መደላድል መፍጠር እንደሚገባ አስቀምጧል።
ህገ መንግስታችን የኢትዮጵያን ህዝቦችን ታሪክና ለዘመናት በመሬት ሳቢያ የደረሰባቸውን በደል እንዲሁም  በአገራችን ህዝቦች ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ህይወት ውስጥ መሬት ያለውን ልዩ ሚና ግምት ውስጥ በማስገባት መሬት የሚመራበት ፖሊሲ የህዝቦችን ተጠቃሚነት ያረጋገጠ እንዲሆን አድርጓል። የገጠርም ሆነ የከተማ መሬትና የተፈጥሮ ሃብት የባለቤትነት መብት የመንግስትና የህዝብ ሆኖ የአርሶ አደሮችና የአርብቶ አደሮችን የመጠቀም መብት ያረጋገጠ እንዲሆን ህገ መንግስቱ ደንግጓል። አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ለኑሯቸው የሚያስፈልጋቸውን መሬት በነፃ የማግኘትና ከመሬታቸው ያለመፈናቀል መብታቸው የተከበረ መሆኑም በግልጽ ተደንግጓል። የኢትዮጵያ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች የመሬት ይዞታቸውን የማልማት፣ የመጠቀም፣  የማከራየትና የማውረስ መብታቸውንም ተጎናጽፈዋል። ህገ መንግስታችን “መሬት የማይሸጥ፣ የማይለወጥ የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች የጋራ ንብረት ነው” በማለት መሬት በጣት ለሚቆጠሩ ባለፀጋዎች ብቻ ሳይሆን ለሰፊው የኢትዮጵያ ህዝቦች አስተማማኝና ዘላቂ የሃብት ምንጭ እንዲሆን ያደረገው። ይህ በመሆኑ በአገራችን መሬትን በመቆጣጠር በጫናና በተጽዕኖ ሊመጣ የሚችለው የፀረ ዴሞክራሲያዊነት በር ተዘግቷል።
የተከበራችሁ የአገራችን ህዝቦች!
ኢሕአዴግ ያስቀመጠው የኢኮኖሚ ልማት አላማ ህዝቡ በየደረጃው ተጠቃሚ የሚሆንበት፣ አገራችንን ከተመጽዋችነት የሚያላቅቅ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እድገት በማረጋገጥ የዳበረ የነጻ ገበያ ኢኮኖሚ መገንባት ነው፡፡ ማንኛውንም አይነት የኢኮኖሚ ልማት ለማረጋገጥ ካፒታል፣ ሰራተኛ የሰው ሃይል፣ መሬትና እነዚህን በውጤታማነት አቀናጅቶ መጠቀም የሚችል አመራር ያስፈልጋል። በአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ሲታይ ልማት ለማረጋገጥ የሚያስችል የካፒታል እጥረት መኖሩና የካፒታል እጥረቱም በአጭር ጊዜ እንደማይፈታም ግልጽ ነው፡፡ በአንጻሩ ቁጥሩ ከፍተኛ የሆነ ታታሪ የሰው ኃይልና ለልማት የተመቸ በቂ መሬት አለ። ይህም በመሆኑ ከፍተኛ ካፒታል የሚጠይቀውን ኢንዱስትሪን ማእከል ያደረገ ልማት የትም እንደማያደረስን የታወቀ ነበር፡፡ በዚህም ምክኒያት ያለንን ሰፊ የሰው ጉልበትና መሬትን እንዲሁም ውስን ካፒታል በመጠቀም የህዝቡ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፈጣን ልማት ለማረጋገጥ የሚያስችል የልማት ስትራቴጂ መከተል የግድ ይል ነበር፡፡ ለዚህም ነው ያለንን አቅም ተጠቅመን አገራችን ከብተና ሊታደግ የሚችል ገጠርንና ግብርና ማእከል ያደረግ ስትራቴጂ በመከተል ልማታችን የጀመርነው፡፡
በ1993 የኢህአዴግ ተሃድሶ ተከትሎ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲና ስትራቴጂያችን ነጥሮ ወጥቶ ተግባራዊ በመደረጉ በአገራችን ለተመዘገበው ፈጣንና ተከታታይ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ባለፉት 23 አመታት ያደረግነው ተግባራዊ እንቅስቃሴ በቀደሙት ስርዓቶች የተረጂነትና የኋላቀርነት መገለጫ ተደርጎ ሲወሰድ የነበረው ግብርናችን የአርሶ አደሩን ህይወት ከመቀየር አልፎ በአገራዊ ኢኮኖሚያዊ እድገቱ ውስጥ ትርጉም ያለው ሚና እንዲጫወት አስችሏል። የሰው ጉልበትን በስፋት በማነቃነቅና መሬትን በአግባቡ በመጠቀማችን ሀገራችን 12 ተከታታይ ዓመታት ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ያስመዘገበች ሲሆን ባለፉት አመታት የግብርና ምርትና ምርታማነትን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደጋችን እንደ ሀገር በምግብ እህል ራሳችንን ችለናል።
የተከተልነው ትክክለኛ ፖሊሲያችን ለህዝባችን የመስራትና የመለወጥ ፍላጎት ልዩ ትኩረት በመስጠቱ ምርታማነታችን ከፍተኛ እድገት እየተመዘገበበት መጓዝ ችሏል። በ1983 ዓ.ም በዋና ዋና ሰብሎች 52 ሚሊየን ኩንታል የነበረውን ዓመታዊ የምርት መጠን ባለፈው አመት 269 ሚሊየን ኩንታል ማድረስ ችለናል። ከዚህ ውስጥ ከ95 በመቶ በላይ የሚሆነው የተመረተው በአነስተኛ የአርሶ አደሩ እርሻ አማካኝነት መሆኑን ሲታሰብ ኢህአዴግ አርሶ አደሩና የግብርናው ዘርፍ የዕድገት ምንጭ እንዲሆን የተከተለውን ፖሊሲ ትክክለኛነት ያረጋግጣል፡፡
የግብርና ምርታችን እያደገ የመጣውን የህዝባችን ቁጥር ከመመገብ አልፎ የውጭ ምንዛሪ በማስገኘት የኢኮኖሚ መሪነቱን ይዞ ዘልቋል። አርሶ አደሩ ከራሱ ፍጆታ አልፎ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያው አቅም እንዲፈጥር አድርገናል፡፡ ለዚህም ስኬት ገበያ መር የአመራረት ስልት መከተላችንና ይህንኑ ለማገዝ የሚያስችሉ የባለሙያ፣ የተቀናጀ አመራርና የግብዓት አቅርቦት ማሟላታችን በምክንያትነት የሚጠቀሱ ናቸው።
በ1994 ዓ.ም 14 ሚሊየን ገደማ የነበረው የተረጂዎች ቁጥር በየዓመቱ እየቀነሰ መጥቶ ባለፈው ዓመት ወደ 2 ነጥብ 7 ሚሊየን ቀንሷል። በቀጣይም የተረጂዎችን ቁጥር ዜሮ ለማድረስ እየተረባረብን እንገኛለን። ይህም ህይወቱ በሚሰፈርለት እርዳታ ላይ ተመሰረቶ የነበረውን ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ የልማት ተሳታፊና ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን ድርቅ በተከሰተ ቁጥር የበርካታ ዜጎች ህይወት ሲቀጠፍበት የነበረውን ሁኔታ በማስቀረት ከፍተኛ ስኬት የተመዘገበበት ነው፡፡  በ1988 .ም በገጠር ከሚኖረው ህዝብ 47 ነጥብ 5 በመቶው በድህነት ውስጥ ይኖር የነበረ ሲሆን የድህነትን ተራራ ለመናድ ባደረግነው ርብርብ ሀገራዊ የድህነት መጠኑ በ2005 .ም ወደ 26 በመቶ ወርዷል፡፡ በያዝነው ዓመት መጨረሻ ደግሞ ቁጥሩ ወደ 22 ነጥብ 2 በመቶ እንደሚወርድ ይጠበቃል።
ቀድሞ ከእጅ ወደ አፍ በሆነ የግብርና ዘይቤ ውስጥ የነበሩ በርካታ አርሶ አደሮች አሁን ዘመናዊ መኖሪያ ቤት ወደ መገንባት ተሸጋግረዋል። በአለባበስ፣ በአመጋገብና በአኗኗር ለውጥ አምጥተዋል። ተንቀሳቃሽና መደበኛ ስልክ፣ የኤሌክትሪክ ሃይል፣ መገናኛ ብዙሃን መጠቀም ጀምረዋል። በሚሊዮኖች የሚቆጠር ሃብት ማፍራት የጀመሩ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮችም በየአካባቢው ተፈጥረዋል። ባፈሩት ሃብት በተለያዩ መስኮች የሚሳተፉ ኢንቨስተሮች ለመሆን በቅተዋል።
ግብርናው በሚያመነጨው ሃብትና ጥሬ ዕቃ ኢንዱስትሪና የአገልግሎት ዘርፎች በፍጥነት እያደጉ ናቸው። ኢኮኖሚያችን ገና ታዳጊ ቢሆንም በእነዚህ ድምር ውጤት ከአንዳንድ የበለጸጉ አገሮች በተሻለ ሁኔታ የሥራ አጥነትን ችግር ተቋቁመን በህዳሴ ጉዞ ወደፊት መገስገስ ቀጥለናል። የመሬት ፖሊሲያችን ለዘመናት የምንታወቅበት የረሃብ ታሪክ እንዲቀየር ከማድረጉም ባሻገር እንደርስበታለን ብለን ባስቀመጥነው ግብ አቅጣጫ ለኢኮኖሚያዊ መዋቅራችን ሽግግር መሰረት እየጣለ ነው።
የተከበራችሁ የአገራችን ህዝቦች!
ኢህአዴግ የተከተላቸው ትክክለኛ ፖሊሲዎች ተጨባጭ ስኬት ማስመዝገብ የቻሉት የአገራችን ህዝቦች ራሳቸው በባለቤትነት የሚያሳተፉበትና ተጠቃሚነታቸውን የሚያረጋግጡበት በመሆናቸው ነው። ኢሕአዴግ ከህዝባዊ ባህሪው በመነጨ የኒዮ ሊብራል ሃይሉንና የአገር ውስጥ የኪራይ ሰብሳቢ ወኪል የሆኑትን ተላላኪዎቻቸውን ጫና በመመከት ነው። የእነዚህ ሃይሎች ወኪል የሆኑት የአገራችን ተቃዋሚዎችም በተጨባጭ የመጣን ለውጥና እድገት ሸምጥጠው በመካድ እርስ በእርሳቸው የሚምታቱ መሰረተ ቢስ የጭፍን ጥላቻ ሃሳቦችን ሲያቀርቡ ይታያሉ። በአንድ በኩል አርሶ አደሩ መሬቱን ገንዘብ ላላቸው ሃብታሞች እንዳይሸጥ በመከልከል መብቱን ገደባችሁት በማለት ተቆርቋሪ መስለው ሊቀርቡ ይሞክራሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ መሬት ለባለሃብት እየተሸጠነው ሲሉ ይሰማሉ፡፡ ከዚህ እርስ በእርሱ ከሚምታታ አቋማቸው መረዳት የሚቻለውም አማራጫቸው ባለፉት ስርቶች ተግባራዊ ሆኖ የወደቀው አርሶ አደሩንና አርብቶ አደሩን በጥቂቶች የጭቆና ቀንበር እንዲጫንበት የሚያደርግ ስርዓትን የሚመልስ መሆኑን ነው፡፡     
በአገራችን መሬት በመንግስትና በህዝቡ እጅ ሆኖ የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ  የመሬት ፖሊሲ መከተላችን ለአጠቃላይ ልማታችን ያለው ጠቀሜታ በተጨባጭ ተረጋግጧል፡፡ በኒዮ ሊብራል ጫና መሬትን በነፃ ገበያ ሰበብ እንደተራ ሸቀጥ እንዲሸጥ ያደረጉ አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገሮችና ሌሎች የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ልማት ለማምጣት እንደ አንድ እንቅፋት ሆኖባቸዋል፡፡ በእንደነዚህ አይነት አገሮች መሬት በተለያየ አጋጣሚ በግለሰቦችና ቡድኖች እጅ በመግባቱ አገሮች የምርት ክንውንንም ሆነ የመንገድ መሠረተ ልማትን የማስፋፋት፣ ለዜጎች የመኖሪያ ቤትና ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማትን ገንብቶ ህዝባቸውን ተጠቃሚ የማድረግ ፍላጎታቸውን መወጣት አልቻሉም። መሬትን ለባለፀጎች ሃብት ማካበቻ እንዲሆን አሳልፈው በመስጠታቸው ወደ ኋላ ተመልሶ መሬትን ለህዝቦቻቸው ልማት የማዋሉን ጉዳይ የማይሞክሩት እየሆነባቸው ይገኛል።
የተከበራችሁ የአገራችን ህዝቦች!
ኢህአዴግ የነደፋቸውና ተግባር ላይ ያዋላቸው እነዚሁ የትክክለኛ የልማት ፖሊሲና ስትራቴጂ ማዕቀፎች ከገባንበት የድህነት አዙሪት ሰብረን እንድንወጣ፣ የአገራችንን ህዝቦች የድህነትና የተረጂነት መጠንን እንድንቀንስ እንዲሁም በከፍተኛ የእድገት ጎዳና እንድንራመድ አስችለውናል፡፡ በአሁኑ ወቅት አገራችን ከሌሎች አገራት ጋር ያላት ግንኙነት ከእርዳታ ወደ ትብብር ማዕቀፍና አብሮ በመልማት ላይ ያተኮረም ሆኗል። ለዚህም ግብርናችን ከፍተኛና ወሳኝ አስተዋፅኦ አበርክቷል።
የግብርናና ገጠር ልማት ስራችን ለዘመናት ተረስቶ በነበረው አርብቶ አደሩም ህይወት ላይ ለውጥ እንዲያስመዘግብ ያደረገው ኢህአዴግ ነው። ኢህአዴግ ለዘመናት ተገልለውና ተረስተው የቆዩ የአርብቶ አደር አካባቢዎችን የመሠረተ ልማትና የማህበራዊ አገልግሎት ተጠቃሚ በማድረግ ፍትሃዊ ልማትን በማረጋገጥ ላይ ይገኛል። የአርብቶ አደሮቻችን ዋነኛ ማነቆ የሆነውን የውሃ አቅርቦት ችግር መቅረፍ በመጀመራችን አርብቶ አደሩ ተረጋግቶ ለመኖር የሚያስችለው ሁኔታ መፈጠር ጀምሯል። በመንደር ማሰባሰብ ፕሮግራሞቻችን አርብቶ አደሮች አንድ ላይ ተረጋግተው እንዲኖሩና ወደ ከፊል አርብቶ አደርነት እንዲቀየሩም ያደረገ ነው።
በገጠሩ አርሶ አደርም ሆነ አርብቶ አደር ህዝባችን ህይወት ላይ የመጡ ለውጦች የትክክለኛው ግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲያችን ስኬቶች ማሳያ ናቸው። በዚህ ሂደት ያስመዘገብነው እድገትና የጀመርነው የህዳሴ ጉዞ ሊሳካ የሚችለው የፖሊሲና ስትራቴጂ ማዕቀፎቻችንን ጠብቀን በመጓዝ ለውጤታማነቱ በስፋት ስንንቀሳቀስ ነው። ኢህአዴግ እንደ እስካሁኑ ሁሉ በግብርናና ገጠር ልማት ስራዎቻችን የገጠሩ ብቻ ሳይሆን የከተሜውም ተጠቃሚነት መረጋገጥ እንዲችል ለስኬት ያበቁንን የፖሊሲና ህዝብን ያሳተፉ የልማት ፕሮግራሞች ጠብቆ በመጓዝ የአገራችንን ህዳሴ እውን ለማድረግ ይሰራል።
ኢህአዴግን በመምረጥ የህዝብ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ የሚገኘውን ፈጣንና ተከታታይ ልማት እናስቀጥል!!

Friday, 27 March 2015

ታላቁ መሪያችን ጓድ መለስ ዜናዊ በ2002 ምርጫ ማግስት ድምፃችን ይከበር ብሎ በነቂስ ወጥቶ በመስቀል አደባባይ ለተሰበሰበው ህዝብ ካደረጉት አይረሴ ንግግር፡-




እኛ ኢህአዴጎች ህዘቡ በነጻ ሞክራሲ ውሳኔው ለሰጠን ይሁንታ እጅግ እናመሰግናለን ፡፡ የአገራችን ሴቶች መቼም ቢሆን የድርጅታችን የጀርባ አጥንት በመሆን እስካሁን ባገኙት የእኩልነት መብት ላይ በመመስረት ለላቀ ውጤት ለመታገል በድምጻቸው መወሰናቸውን በእጅጉ አናደንቃለን ፤እናመሰግናለም፡፡
የአገራችን ወጣቶች ባለፉት አመታት በተገኘው ልማት ተጠቃሚ የሆኑ ብቻ ሳይሆኑ ውጤቱንም ለማጣጣም በስራ ፈላጊነት የሚጠባበቁትን ቢሆኑ የችግራቸው መፍትሄ የድርጅታችን መስመር መሆኑን ተገንዝበው በአስገራሚ ደረጃ ይሁኝታቸውን ስለሰጡን በእጅጉ እናመሰግናለን፤እንኮራባቸውማለን፡፡
በምርጫው አመትም ቢሆን አማራጭ የሌለውን የመንግስት ግብር መክፈል አለባችሁ ብለን አጥብቀን የያዝናቸው ከዛም አልፈን በአንዳንድ የአፈፃፀም ስህተቶቻችን ቅር ያሰኘናቸው ባለሃብቶች ሳይቀሩ ድርጅታችን ከስህተቶቹ የሚማርና ጉድለቶቹን የሚያስተካክል ድርጅት መሆኑን ተገንዝበው ለሰጡን ድምፅና ድጋፍ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡
ከሰፊው የከተሞቻችን ህዝብም ባሻገር መላው የአርሶ አደር ህዝባችን እንደ ወትሮው ራሱንና ድርጅታችንን እንደማይነጣጠሉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች አድርጎ በመቁጠር የማይናወጥ አቋሙን በድጋሚ በምርጫ ካርዱ በማረጋገጡ የሚሰማን ክብርና ድስታ ወሰን የለውም ፡፡

የአዲስ አበባ ህዝብ በማንኛውም ወቅት ለህዝቡ ድምፅ ያለንን ክብርተመልክቶ ቅሬታ የሚፈጥሩበትን ጉድለቶቻችንን ለማረም ያለንን ቁርጠኝነትና ገና በቀጣይ ማስተካከል ያለብን ነገሮች እንደተጠበቁ ሆኖ ያስመዘገብነውን ድልና ውጤት ተገንዝቦ ከአምስት አመት በኋላ ብይኑን እንደገና በነፃ ምርጫው ሰጥቶናል፡፡የአዲስ አበባ ህዝብ ድምፁን ሲነፍገንም ሆነ ድምፁን ሲሰጠን ከመብትና ጥቅሙ በመነሳት እጅግ ፍትሃዊ የሆነ ብይን የሚሰጥ ህዝብ እንደሆነ በተግባር አረጋግጧል፡፡የመጨረሻውና ፍትሃዊ ዳኛ ለሆነው ህዝባችን ያለንን ክብርና ምስጋና በድጋሚ ለመግለፅ እፈልጋለሁ፡፡
በዘንድሮው ምርጫ የአዲስ አበባ ህዝብና በአጠቃላይም የኢትዮጵያ ህዝብ ለኢህአዴግ ጥረትና የስራ ውጤት እውቅና ከመስጠት አልፎ ለተቃዋሚ ፓርቲዎች የማያሻማ መልእክት አስተላልፏል ብዪ አምናለሁ፡፡ህዝብን ለማገልገል የሚያስችል ራእይ ይዞ ከመንቀሳቀስ ይልቅ የጭፍን ጥላቻ ፖለቲካን ማስተናገድ እንደማይፈልግ፤የህዝብ ጥቅምን ሳይሆን የቂም በቀልና ቁርሾ አላማን የሚያራምድ ፖለቲካን ማየት እንደማይፈልግ፤ከሁሉም በላይ ደግሞ በምርጫ ሽፋን የአንድ ሰው ህይወትም ቢሆን መክፈል እንደማይፈልግ በውል አቋሙን ገልጿል ብዪ አምናለሁ፡፡
ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከድርጅታችን ልምድ ሊወስዱት የሚገባ ትምህርት ያለ ይመስለኛል፡፡የህዝቡን ብይን ሰበብ አስባብ ሳይፈልጉ በፀጋ ሊቀበሉ፤ህዝብ ያልወደደላቸው ነገር ምን እንደሆነ በሰከነ አእምሮ አጢነው ለማስተካከል ቆርጠው ቢነሱ ህዝቡ ፍትሃዊ ዳኛ እንደሆነ በተደጋጋሚ አስመስክሯልና በሚቀጥለው ጊዜ ውጤታቸውን አይቶ ሊክሳቸው እንደሚችል ሊገነዘቡ ይገባል እላለሁ፡፡እናም እስካሁን ድረስ ይህንኑ ገንቢ አቅጣጫ ለመከተል ለወሰኑት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ያለኝን አድናቆት እየገለፅኩ ሌሎቹም ይህንን ፈለግ እንዲከተሉ በህዝቡ ስም እጠይቃለሁ፡፡በከፊል መገለፅ በጀመረው የምርጫ ውጤት እንደታየው ህዝቡ ድምፅ እንደነፈጋቸው በፀጋ በመቀበል የዚህን ኩሩ ህዝብ ብይን ከቶውንም ተፈፃሚነት በማይኖረው የውጭ ሃይሎች ይግባኝ ሰሚነት ለመሸርሸር ከመሞከር እንዲቆጠቡና ለራሳቸውና ለህዝባቸው ውሳኔ ተገቢውን ክብር እንዲሰጡ አሳስባለሁ፡፡
እስካሁን ድረስ በነበረው ሂደት አንዳንድ የፖለቲካ ሃይሎች የተጫወቱት አፍራሽ ሚና ከማናችንም የተሰወረ አይደለም፡፡በምርጫው እለት ታዛቢ ተወካዮቻቸው

ባለፈው ምርጫ ምርጫችንን በመታዘብ ከወገንተኝነት ነፃ ሆነው እንዲመሰክሩ እምነታችንን የጣልንባቸው ታዛቢዎች ወገን ለይተው ሊፋለሙና በእሳት ላይ ነዳጅ ሲያርከፈክፉ በከፍተኛ ቁጭት ተመልክተናል ፡፡ ወዳጅና አጋር እንዲሆኑን የተመኘናቸው አንጋሽ መሆን ሲከጅላቸው ፣የኢትዮጵያ ፖለቲካ የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት መሆን ሲቃጣቸው በከፍተኛ ሃዘን ተመልክተናል ፡፡ አሁንም ያለፈው አልፏል ፡፡ በዚህ ኩሩ ህዝብ የወዳጅነትና አጋርነት እጆች አሁንም እንደተዘረጀጉ ናቸው ፡፡ የህዝቡን መሪዎቹን የመምረጥ ሉዓላዊ ስልጣን አክብሩ ፣ ለህዝቡ ውሳኔና ድምፅ ተገቢውን ክብር ስጡ እንላለን ፡፡
የተከበራችሁ የሰላምና የዴሞክራሲ ሰልፈኞች !   
በዘነድሮው ምርጫ ህዝባችን እስካሁን ከተገለፀው ጊዜያዊ ውጤት በመነሳት ይሁንታን እንደሰጠን ግልፅ ቢሆንም ይሁንታቸውን ያልሰጡን ዜጎቻችን እንዳሉም እንገነዘባለን ፡፡ የመረጠንን ህዝብ ድምፅና ውሳኔ እንደምናከብር ሁሉ ያልመረጠንን ህዝብ ድምፅም እንደምናከብር ያለአንዳች ማወላወል ለመግለፅ እወዳለሁ ፡፡ እናም ይሁንታችሁን ያልሰጣችሁንን ዜጎች ቅር ያሰኘንበትን ምክንያት አጥንተን ለማስተካከል እንደምንረባረብ ፣ በሚቀጥለው ጊዜ ይሁንታችሁን ለማግኘት ሌት ተቀን እንደምንጣጣር እስከዚያው ድረስ ደግሞ የምናቋቁመው መንግስት የመረጠንን ህዝብ ብቻ ሳይሆን እናንተንም በእኩልነት እንደሚያገለግል በድርጅታችን መላ አባላትና ሰማዕታት ስም ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ ፡፡
ምንም አንኳ ህዝባዊ አላማችንና የተደራጀ ርብርባችን ባስገኘልን ታላቅ ህዝባዊ ድጋፍ የምንኮራና የምንደሰት ብንሆንም ህዝቡ እጅግ ከባድ ሃላፊነት በላያችን ላይ እንደጫነም በሚገባ እንገነዘባለን ፡፡ ምንም አንኳ በጥረታችንና በውጤታችን ህዝባችንን በማርካታችን ብንደሰትም አሁንም ህዝባችንን ቅር የሚያሰኙ በርካታ መሰረታዊ ጉድለቶች እንዳሉብን በጥልቀት እንገነዘባለን ፡፡ ስለሆነም በዛሬው የዴሞክራሲ ፌሽታ እለት እኛ ኢህአዴጎች ድምጽ ለሰጠንም ሆነ ላልሰጠን ፍትሃዊ ዳኛ ህዝባችን ያለንን ጥልቅ አክብሮትና ምስጋና በድጋሚ ከልብ እንገልፃለን ፡፡
ምንም እንኳ የምርጫውን ውጤት ሙሉ በሙሉ ከማወቃችን በፊትም ቢሆን በሚቀጥሉት አምስት አመታት የህዝባችንን ፍላጎት ያረካሉ ብለን የቀየስናቸው አቅጣጫዎችና እቅዶች ያሉን ቢሆንም ያገኘነውን እጅት ሰፊ የህዝብ አደራ ታሳቢ በማድረግ እነዚህን እቅዶች ለመተግበር ከመረባረብ ጎን ለጎን የሰጣችሁንን ከፍተኛ ሃላፊነት በይበልጥ መለወጣት ከነገው እለት ጀምሮ እቅዶቻችንን በዝረዝር ፈትሸን መከለስ እነደምንጀምር ላረጋግጥላችሁ እፈልጋለሁ ፡፡በዚህ አጋጣሚ ያገኘነው ከግምታችን በእጅጉ የላቀ ውጤት ተጨማሪ ከባድ ሸክም ያሸክመን እንደሆነ እንጂ እንደማያኩራራን እንደገና ላረጋጥጥላችኑ እፈልጋለሁ ፡፡
 በምርጫው ያልተሳካላችሁ ተቃዋሚዎች ሁሉ የህዝቡን ድምፅና ውሳኔ ተቀብላችሁ የአገሪቱን ህገ-መንግስትና ህጎች አክብራችሁ እስከተንቀሳቀሳችሁ ድረስ የምክር ቤት ወንበር ቢኖራችሁም ባይኖራችሁም በሁሉም ወሳኝ አገራዊ ጉዳዮች እናንተን ለማማከርና ለማሳተፍ ቃል እንገባላኋላን፡፡ይህን ቃል የምንገባላችሁ በአገራችን የተሃድሶ ትግል አጋር መሆን እደምትችሉና እንደሚገባችሁ ስለምናምን ብቻ ሳይሆን ፣ ምንም ያህል ቁጥር ይኑራቸው ድምፃቸውን ለእናንተው የሰጡ ዜጎች በወሳኝ አገራዊ ጉዳዮች ላይ የመሳተፍና የመደመጥ መብት እነዳላቸው ጠንቅቀን ስለምናውቅ ጭምር ነው ፡፡ በዛሬው ምርጫ አሸናፊው ይህኛው ወይም ያኛው ድርጅት ሳይሆን አሸናፊው የኢትዮጵያ ህዳሴ ፣አሸናፊው የኢትዮጰያ ዴሞክራሲና የኢትዮጵያ ህዝቦች በመሆናቸው ድሉ የሁላችንም ነው፡፡በመሆኑም ለመላው መራጭ ህዝባችንና የአገራችን የሰላምና የዴሞክራሲ ሃይሎች ከልባችን እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን ፡፡
በድጋሚ በሉዓላዊው የመሾምና የመሻር ስልጣናችሁ ፊት ከአምስት ሚሊዮን በላይ የምንሆን የኢህአዴግ አባላትና ሰማዕታት በታላቅ ትህትና ምስጋናችንን እንገልፃለን ፡፡ እጅ እንነሳለን