ህዳሴ፡-
በቅድሚያ ለቃለምልልሱ ስለተባበሩን በአንባቢያን ስም ከልብ እናመሰግናለን፡፡ በከተማችን የሚ ስተዋለው የመልካም አስተዳደር ችግር
ምንጩ ምንድነው ይላሉ?
አቶ
ይስሀቅ፡- እኔም አመሰግናለው፡፡ ከትርጉሙ ስንነሳ መልካም አስተዳደር ዘርፈ ብዙ ትርጉም ነው ያለው፡፡ መልካም አስተዳደር ሲባል
የህግ የበላይነትን ማረጋገጥ ነው፣ ግልፅነት፣ የተጠቃሚነት ስርአት ማስፈን ነው፣ የህዝብ ተሳታፊነትንና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ነው፣
ዋና ዋና በሆኑት የልማት እና የሰላም ጉዳዮች መግባባት መፍጠር ነው፡፡ እንዲህ ሰፋ ያለ ትርጓሜ ያለው ነው”” በተጨማሪ መልካም
አስተዳደር ሲባል መልካም ስራን ከመስራት ይመነጫል”” ህዝቡ የሚጠይቃቸው ጥያቄዎችን አግባብ ባለው መልኩ ህግና ስርአትን በመጠበቅ
ፈጣን የሆነ ምላሽ መስጠት ነው”” በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ጉዳዮችም ህዝቡን በቅንነት ማገልገል ነው፡፡ ህዝብን
ማገልገል ክቡር እንደሆነ አስቦ መስራት ነው፡፡ ስለዚህ እነዚህን ነጥቦች በምናይበት ጊዜ የመልካም አስተዳደር ችግር ምንጮችን ስንመለከት
ብዙ ናቸው”” ዋና መሰረቱ በየደረጃው ያለ አመራር የተመደበው ህዝብን ለማገልገልና የህዝብ ችግርን ለመፍታት ነው፡፡ የህዝብ ወገንተኛ
መሆን አለበት፡፡ ስለዚህ ችግሮች እየተፈጠሩ ያሉት የህዝብ ወገንተኛ ከመሆን ጋር የሚመነጩ ናቸው”” ህዝቡ መበደል፣ መሰቃየት የለበትም
የሚል የህዝብ ወገንተኝነት ማጣት ነው፡፡ በየደረጃው ያለ አመራር የህዝብ አገልጋይነት ስሜቱ በሚፈለገው ደረጃ አለመሆኑ ነው፡፡
በየደረጃው ያለው የመንግስት ሰራተኛ የተቀጠረው ህዝብን ለማገልገል መሆኑን በተመለከተ የተሟላ እምነት ይዞ አለመስራት ነው፡፡ ሁለተኛው
እላፊ ተጠቃሚነት ነው፡፡ ይህ ማለት የመንግስት እምነት በከተማው ልማታዊ ፖለቲካል ኢኮኖሚ መመስረት ነው፣ ይህ ማለት ህብረተሰቡ
በየደረጃው የልማቱ ተጠቃሚ የሚሆንበትን ፍትሀዊ የሆነ የልማት ተጠቃሚ የሚሆንበት ሁኔታ መፍጠር ነው፣ ስለዚህ ልማታዊ ፖለቲካል
ኢኮኖሚ እንደስርአት መመስረት አለበት”” ይህ ማለት አንዱ ተጠቃሚ
ሌላው የበይ ተመልካች የሚሆንበት ሳይሆን ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል የሚያጠቃልል ስርአት መፍጠር ማለት ነው፡፡ አሁን በከተማው
የኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰቡ በአመለካከትም በተግባርም የበላይ ሆኖ መልካም አስተዳደርን ማስፈን ትልቅ ፈተና እየሆነ ነው ያለው፡፡
ቁጥራቸው ጥቂት ቢሆንም ባይሆንም ህብረተሰቡን የሚያጉላሉት የሚፈልጉት ነገር ስላለ ነው፡፡ በተቀመጠው አሰራርና ህግ መሰረት ከማገልገል
ውጪ አገልግሎትን በገንዘብ በጉቦ በመጠየቅ ለመጨረስ የመፈለግ አመለካከት በሲቪል ሰርቪሱም በአመራሩም ስላለ ታግለን ስላላስተካከልን
ነው፡፡ ስለዚህ ምንጮቹን በእነዚህ ሁለት መንገዶች መውሰድ እንችላለን፡፡ አንደኛው እላፊ መፈለግ፣ ሁለተኛው እላፊ ባይፈልግም በተቀመጠው
አሰራር መሰረት አመራሩና ፈፃሚው ህብረተሰቡን የማገልገል ክፍተት ነው፡፡